ኤ ቢ ዋይ ኤስ ኃ/የተ/የግል ማህበር በ2012 እ.ኤ.አ የተቋቋመ ድርጅት ሲሆን አለም አቀፍ የምግብ ደህንነት መስፈሮቶችን ሁሉ ያሟሉ ምግቦችን በፋብሪካ በማቀነባበር ለአለም አቀፍ እና ለሀገር ውስጥ ገበያ ያቀርባል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ከ500 በላይ ቋሚ እና ጊዜያዊ ሠራተኞቹን በዋናው ቢሮ እና ሱቆቹ (አዲስ አበባ)፣እንዲሁም በፋብሪካውቨእና ሱቆቹ (ሱሉልታ) በመቅጠር ስራውን እየሠራ ይገኛል፡፡
ድርጅቱ አብረውት ሊሠሩ የሚፈልጉ ተጨማሪ ሴት የሽያጭ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡ የሽያጭ ሠራተኛዋ የድርጅቱን ምሮቶች በድርጅቱ ሱቅ ውስጥ የማስተዋወቅ፣ የመሸጥ፣ የማሻሻጥ፣ ንብረት (ገንዘብ እና ሸቀጥ) ተረክቦ ህጋዊ የንብረት አስተዳደር እና የሀገሪቷን የሽያጭ ህግ በመከተል ሸቀጥ ለደንበኞች በታማኝነት ታስረክባለች ፤ ገንዘቡን እና ህጋዊ ሠነዶችን ደግሞ ለድርጅቱ በየቀኑ እንዲደርሰው ታደርጋለች፡፡
ዝርዝር የሥራ ተግባር እና ኃላፊነት
- የተረከበችውን የሱቅ ካዝና (safe box) እና ቁምሳጥኖች ቁልፎች በአግባቡ መያዝ
- የድርጅቱን ምርቶች በየቀኑ ቆጥራ መረከብ
- የድርጅቱን ምርቶች ማስተዋወቅ
- የድርጅቱን ምርቶች መሸጥ
- የድርጅቱን ምርቶች ስትሸጥ የመንግስት የግብይት ህጎችን መከተል፣ ደረሠኝ መቁረጥ፣ መሠነድ እና ለቅርብ ኃላፊና ለኦዲት ማስረከብ
- የሽያጭ ሪፖርት በየቀኑ፣ በየሣምንቱ እና በየወሩ ማቅረብ
- የደንበኞችን አስተያየት መሰብሰብ እና ምላሽ መስጠት እንዲሁም ለቅርብ አለቃ አስተያየቶችን በመላክ እና ግብረ መልስ ተቀብላ ለደንበኞች መግለፅ
- የተረከበችውን የሥራ መገልገያ ቁምሳጥን ለምሳሌ የሽያጭ መመዝገቢያ ማሽን በአግባቡ መያዝ እና መገልገል
- የንብረት ቆጠራ ከመካሄዱ በፊት ለቆጠራ በሚያስፈልጉ ዝግጅቶችን አስቀድሞ ማድረግ (እቃ በአይነት ለይቶ መያዝ፣ መደርደር፣ መመዝገብ፣ የተሸጠውን የሽያጭ አይነት ብዛት በቁጥር እና በገንዘብ አስልታ አዘጋጅታ ከተዛመዱ ሠነዶች ጋር አመሳክራ፣ ባላንሥ ሠርታ፣ ጉድለት ካለ ለይታ ማዘጋጀት) ከዚያም ቆጠራውን ማካሄድ
- ለረዳት የሽያጭ ሠራተኞች ሥልጠና መስጠት
- የስልክ ልውውጦችን በአግባቡ መከወን
- ተጨማሪ ስራ በአለቃዋ ስትታዘዝ መስራት